ሞሮኮ የታሰሩ ሶስት የሴኔጋል ደጋፊዎችን ፈታች

- Advertisement -
Sidebar AD

​#FastMereja I በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ ወቅት በተቀሰቀሰ ረብሻ ታስረው ከነበሩት 18 የሴኔጋል ደጋፊዎች መካከል ሶስቱ ከእስር ተለቀዋል።

​በራባት ከተማ በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ላይ በተከሰተ ግጭት ተሳትፈዋል በሚል በሞሮኮ ፍርድ ቤት ተፈርዶባቸው የነበሩት ደጋፊዎች፣ የሦስት ወራት የእስር ቆይታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ መፈታታቸው ተረጋግጧል። የሴኔጋል መከላከያ ጠበቃ ፓትሪክ ካቦው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው (X) ባስተላለፉት መልዕክት፣ የሀገሪቱ ዲፕሎማቶች ባደረጉት ጥረት ሶስቱ ዜጎቻቸው መለቀቃቸውን ገልጸዋል።

​እንደ ኤኤፍፒ (AFP) ዘገባ፣ በወቅቱ በተፈጠረው ሁከት በአጠቃላይ 18 የሴኔጋል ዜጎች ተከሰው የእስር ቅጣት ተላልፎባቸው የነበረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት 15 ደጋፊዎች አሁንም በሞሮኮ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ ይገኛሉ። ቀሪዎቹ እስረኞች መቼ ሊፈቱ እንደሚችሉ እስካሁን በግልጽ የታወቀ ነገር የለም።


Source: FastMereja

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: