በግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ ሲፈለግ የነበረው ሻለቃ ያምራል በቁጥጥር ስር ዋለ !ባለፈው ሳምንት ሚያዚያ 6 ቀን 2018ዓ.ም ባህ…

- Advertisement -
Sidebar AD
በግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ ሲፈለግ የነበረው ሻለቃ ያምራል በቁጥጥር ስር ዋለ !
ባለፈው ሳምንት ሚያዚያ 6 ቀን 2018ዓ.ም ባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 06 “መኳንት ስለሽ ” በተባለ ሆቴል ተቀጥራ ትሰራ የነበረችውን ማህሌት ማሩ የተባለችውን ወጣት የአማራ ክልል አድማ ብተና አባል ነው በተባለው እና ስሙ ሻለቃ ያምራል አለሙ የተባለው ተጠርጣሪ ከሌሎች ግብረአበሮቹ ጋር በመሆን ከስራ ቦታዋ አስገድደው ወደ ሌላ ሆቴል በመውሰድና አስገድ ዶ ከደፈራት በኃላ በሆቴሉ ውስጥ የግድያ ወንጀል ፈፅሞ መሰወሩን የአካባቢው የአይን እማኞችና ጏደኞቿ በማህበራዊ ሚዲያ ሲያሰራጩ መሰንበታቸው ይታወሳል ።
የአማራ ክልል ፖሊስም የሰው ህይወት አጥፍቶ የተሰወረውን ግለሰብ ፎቶግራፍን ጭምር በማህበራዊ ሚዲያ ሲያፈላልግ ቆይቷል ።
ሆኖም በዛሬው እለት የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በሰው ሕይወት ማጥፋት ወንጀል ተጠርጥሮ ለተወሰነ ጊዜ ተሰውሮ የነበረው ያምራል አለበል አለሙ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልፆል ::
ተጠርጣሪ ያምራል አለበል አለሙ ወንጀሉን ፈጽሞ ከአካባቢው ቢሰወርም፣ በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እንዲሁም በክልሉ የፀጥታ ኃይሎች በተደረገ የተቀናጀና ጥብቅ ክትትል ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን በፌስ ብክ ገፁ አስነብቧል ::
@seledadotio
@seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: