የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የጦር መሣሪያዎችን በዘመናዊ ዳታቤዝ መመዝገብ ጀመረ ፌደራል ፖሊስ በተቋሙ ግምጃ ቤትና በአባላቱ እጅ …

- Advertisement -
Sidebar AD
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የጦር መሣሪያዎችን በዘመናዊ ዳታቤዝ መመዝገብ ጀመረ
ፌደራል ፖሊስ በተቋሙ ግምጃ ቤትና በአባላቱ እጅ የሚገኙ የጦር መሣሪያዎች ላይ ምልክት የማድረግና ወደ ዘመናዊ የመረጃ ቋት የማስገባት ሥራ በይፋ መጀመሩን አስታውቋል።
አዲሱ አሠራር በሀገር አቀፍ ደረጃ የትኛው የጦር መሣሪያ የት እንደሚገኝ በቀላሉ ለማወቅና ለመቆጣጠር ያስችላል ተብሏል።
ምልክት የማድረጉ ሥራ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውርን ለመግታት፣ የጠፉ መሣሪያዎችን ለመለየትና በጦር መሣሪያ የታገዙ ወንጀሎችን ለመመርመር ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ተጠቁሟል።
የምዝገባ ሶፍትዌሩና የመረጃ ቋቱ በፌደራል ፖሊስ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የበለፀገ መሆኑ ተመላክቷል።
👉 በፌደራል ደረጃ የተጀመረው ይህ ምዝገባ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደር ፖሊስ ተቋማት ውስጥ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።ስፑትኒክ
@seledadotio
@seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1