ዳንኤል ክብረት የብልጽግና ፓርቲ እጩ ሆነው ለምርጫ ቀረቡ

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | በስደስተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ በግላቸው ተወዳድረው ፓርላማ የገቡት ዳንኤል ክብረት፣ ዘንድሮ በሚካሄደው ሰባተኛው ምርጫ ግን ብልጽግናን ተቀላቅለዋል፤ እጩ ሆነውም ቀርበዋል።

በእርግጥ በ2013ቱ ምርጫም ብልጽግና በአዲስ አበባ ዕጩ ያላቀረበበት የምርጫ ክልል ዳንኤል የተወዳደሩበት ብቻ ነበር።

ምንም እንኳን የእንደራሴዎች መቀመጫን አሸንፈው በግላቸው ፓርላማውን ቢቀላቀሉም ቢያንስ አዲስ ማለዳ ተገኝታ በተከታተለቻቸው እና በቀጥታ ሥርጭት በተላለፉ መደበኛም ይሁን አስቸኳይ ስብሰባዎች ላይ ዳንኤል ጥያቄ ሲያቀርቡ አልያም አስተያየት ሲሰጡ አልተስተዋለም።

ዳንኤል የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ መሆናቸውም ይታወቃል ስትል የዘገበችው አዲስ ማለዳ ናት።

Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
##getutemesgen #getu


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: