ሸገር ደርቢ በፍፁም ስፖርታዊ ጨዋነት መጠናቀቁን ፖሊስ ገለፀ

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ ድምቀት የሆነው እና ለ51ኛ ጊዜ የተደረገው የሸገር ደርቢ ውድድር ፍፁም ስፖርታዊ ጨዋነት በተሞላበት ሁኔታ መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።

በአዲስ አበባ ስታዲየም የተደረገው የኢትዮጵያ ቡና እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታ፣ ኢትዮጵያ ቡና 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

በዚህ የደርቢ ጨዋታ ስፖርታዊ ጨዋነትን በጠበቀ መልኩ እንዲካሄድ የሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች፣ የደጋፊዎች ማህበር አመራሮች፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን እንዲሁም የፌደራል እና የከተማው የፀጥታ አካላት ሚናቸው የጎላ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።

Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #nbc


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2