በኮንትሮባንድ ወደ ሀገር የገቡ ከ500 በላይ ተንቀሳቃሽ ስልኮች ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ዋሉ።

- Advertisement -
Sidebar AD

ያሬድ ባዬ እና መለሠ ማሩ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸሙት ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 7 ሰዓት 30 በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አዲስ አበባ የገበያ ማዕከል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።

ተጠርጣሪዎቹ ተገቢውን የጉምሩክ ሂደት ሳያልፉ በኮንትሮባንድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ 5 መቶ 41 ተንቀሳቃሽ ስልኮችን ሌላ ዕቃ በማስመሠል በካርቶን ተሸክመው እየተንቀሳቀሱ ሳለ በአካባቢው በስራ ላይ የነበሩ የፖሊስ አባላት በመጠራጠር ባደረጉት ፍተሻ ከነ ኤግዚቢቶቹ በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

ህጋዊ አግባብነት የጎደላቸው የንግድ እንቅስቃሴዎች የሀገርን ምጣኔ ሀብት ከመጉዳት ባለፈ በህጋዊ ነጋዴዎችና በንግድ ስርዓቱ ላይ የሚፈጥሩት ጫና ከፍተኛ እንደሆነ በመገንዘብ ሁሉም ዜጋ መሠል ድርጊቶችን ማውገዝ እንደሚገባው የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጥሪውን አስተላልፏል።

Addis Ababa police





Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2