የትግራይ የመገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ስራ አስኪያጅ በተሾሙ በ45 ቀናት ውስጥ ከኃላፊነት መነሳታቸው ምንጮች ገለፁ።
ለስራ አስኪያጁ ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደገለፁት የካቲት 30/2018 ዓ/ም የኤጀንሲው ስራ አስኪያጅ ሆኖው የተሸሙት አባዲ ገ/ስላሴ ከሃላፊነታቸው ተነስተዋል።
ሚያዝያ 16/2018 ዓ.ም በፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) የተፃፈው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው ሃላፊው በሁለት መስመር ፅሁፍ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርገዋል።
ሃላፊው በተሾሙ በ45 ቀናት ውስጥ ለምን ከሃላፊነት እንደተነሱ በደብዳቤው በግልፅ ባይቀመጥም ስራ አስኪያጁ ” ወደ ህወሓት በማዳላት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራ አደናቅፈዋል ” በሚል ምክንያት እንደሆነ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቁመዋል።
ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ሚያዝያ 13/2018 ዓ.ም ለሚድያ የሰጡት መግለጫ በክልሉ መንግስታዊ ሚድያዎች ተዛብቶ መሰራጨቱ በመግለፅና በመወቀስ Landa Report እና ላዛ ትግርኛ ለተባሉ የግል ሚድያዎች ሚያዝያ 14/2018 ዓ.ም ተጨማሪ ማስተካከያና ማብራርያ መስጠታቸው ይታወሳል።
ቴሌቪዥን ጣብያው የፕሮግራሞች ዳይሬክተር ጋዜጠኛ አፈወርቂ ገ/ሂወት የስራ አስኪያጁ ስራ ደርበው እንዲሰሩ ከፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ደብዳቤ እንደደረሳቸው ሰምተናል።
አባዲ ገ/ስላሴ ከጦርነት በፊት እና በኋላ የትግራይ ቴሌቬዥንን ለረጅም ዓመታት የመሩት ተሻለ በቀለ ተክተው መሾማቸው መዘገባችን ይታወሳል።
@tikvahethiopia

Source: Yeneta Tube









No comments yet.