ከ87 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ አንድ ሺህ 452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በስድስት ቢሊዮን ብር ወጪ ሊገነቡ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ምንም ዓይነት የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በሌለባቸው ወረዳዎች 1 ሺህ 452 አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እንቅስቃሴ ተጀምሯል።
የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሎች ትብብር የሚከናወን ይሆናል ብለዋል።
ይህ የግንባታ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ 87 ሺህ 120 ተማሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሲሆን፤ ይህም በከተማና በገጠር ለሚገኙ የኢትዮጵያ ልጆች እኩል የትምህርት ዕድልን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን አስታውቀዋል።
የግንባታ ስራው ከአዲስ አበባ ከተማ ውጪ በሁሉም ክልሎች ይተገበራል። በዛሬው ዕለትም በትምህርት ሚኒስቴርና በክልል ትምህርት ቢሮዎች መካከል የስምምነት ፊርማ ተፈርሟል።
#ጋዜጣ_ፕላስ
Source: Yeneta Tube









No comments yet.