በሚስቱ የተቆረጠው የወንድ ብልት በስፌት ተቀጠለ
በአርሲ ዞን በትዳር አጋራቸው ጥቃት ደርሶባቸው ሙሉ በሙሉ ተቆርጦ የወደቀው የ42 ዓመት ጎልማሳ ብልት፣ በአሰላ ሪፈራል ሆስፒታል በተደረገ የ3 ሰዓታት ስኬታማ ቀዶ ህክምና ተመልሶ መገጠሙ ተነገረ።
ድርጊቱ የተፈጸመው ከአንድ ወር በፊት ሲሆን፣ በግለሰቡና በባለቤታቸው መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ምክንያት ባለቤታቸው እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ላይ በስለት ሙሉ በሙሉ በመቁረጥ መሬት ላይ ጥለውታል። የ6 ልጆች አባት የሆኑት ተጎጂው፣ የተቆረጠውን ብልታቸውን በፌስታል ጠቅልለው በመያዝ በራሳቸው ጥረት በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል መድረሳቸው ታውቋል።
የኩላሊትና የሽንት ቧንቧ ስፔሻሊስት ዶ/ር ፍቃዱ ሀብታሙ እንደገለጹት፣ ህክምናው የተከናወነው ጉዳቱ በደረሰ በ3 ሰዓት ውስጥ ግለሰቡ ሆስፒታል በመድረሳቸው ነው። በጥንቃቄ ለ3 ሰዓታት በተደረገ ስፌት ብልቱ ወደ ቦታው የተመለሰ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ተጎጂው በሽንት ቧንቧቸው በኩል መሽናት መጀመራቸውንና የጤና ሁኔታቸው በመሻሻል ላይ መሆኑን አረጋግጠዋል።
እንዲህ ዓይነት ጉዳት ሲያጋጥም በ6 እና በ8 ሰዓታት ውስጥ ሆስፒታል መድረስ ለስኬታማነቱ ወሳኝ ነው ተብሏል። ብልቱ የመቆም እና የግብረ-ሥጋ ግንኙነት የመፈጸም እድሉ ከፍተኛ ቢሆንም፣ እንደ ቀድሞው ሙሉ ጥንካሬ ላይኖረው እንደሚችል ተገልጿል።
የተቆረጠው አካል በንጹህ ፌስታል ተጠቅልሎ ሳይቆሽሽ በፍጥነት ወደ ህክምና ተቋም መወሰድ አለበት።
ተጎጂው በአሁኑ ወቅት በሆስፒታል ክትትል ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ ለደህንነታቸውና ለግል ሚስጥራቸው ሲባል ማንነታቸውና ዝርዝር አድራሻቸው እንዳይገለጽ ተደርጓል ሲል ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ዘግቧል።
ምስል ኤአይ
@seledadotio
@seledadotio
በአርሲ ዞን በትዳር አጋራቸው ጥቃት ደርሶባቸው ሙሉ በሙሉ ተቆርጦ የወደቀው የ42 ዓመት ጎልማሳ ብልት፣ በአሰላ ሪፈራል ሆስፒታል በተደረገ የ3 ሰዓታት ስኬታማ ቀዶ ህክምና ተመልሶ መገጠሙ ተነገረ።
ድርጊቱ የተፈጸመው ከአንድ ወር በፊት ሲሆን፣ በግለሰቡና በባለቤታቸው መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ምክንያት ባለቤታቸው እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ላይ በስለት ሙሉ በሙሉ በመቁረጥ መሬት ላይ ጥለውታል። የ6 ልጆች አባት የሆኑት ተጎጂው፣ የተቆረጠውን ብልታቸውን በፌስታል ጠቅልለው በመያዝ በራሳቸው ጥረት በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል መድረሳቸው ታውቋል።
የኩላሊትና የሽንት ቧንቧ ስፔሻሊስት ዶ/ር ፍቃዱ ሀብታሙ እንደገለጹት፣ ህክምናው የተከናወነው ጉዳቱ በደረሰ በ3 ሰዓት ውስጥ ግለሰቡ ሆስፒታል በመድረሳቸው ነው። በጥንቃቄ ለ3 ሰዓታት በተደረገ ስፌት ብልቱ ወደ ቦታው የተመለሰ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ተጎጂው በሽንት ቧንቧቸው በኩል መሽናት መጀመራቸውንና የጤና ሁኔታቸው በመሻሻል ላይ መሆኑን አረጋግጠዋል።
እንዲህ ዓይነት ጉዳት ሲያጋጥም በ6 እና በ8 ሰዓታት ውስጥ ሆስፒታል መድረስ ለስኬታማነቱ ወሳኝ ነው ተብሏል። ብልቱ የመቆም እና የግብረ-ሥጋ ግንኙነት የመፈጸም እድሉ ከፍተኛ ቢሆንም፣ እንደ ቀድሞው ሙሉ ጥንካሬ ላይኖረው እንደሚችል ተገልጿል።
የተቆረጠው አካል በንጹህ ፌስታል ተጠቅልሎ ሳይቆሽሽ በፍጥነት ወደ ህክምና ተቋም መወሰድ አለበት።
ተጎጂው በአሁኑ ወቅት በሆስፒታል ክትትል ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ ለደህንነታቸውና ለግል ሚስጥራቸው ሲባል ማንነታቸውና ዝርዝር አድራሻቸው እንዳይገለጽ ተደርጓል ሲል ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ዘግቧል።
ምስል ኤአይ
@seledadotio
@seledadotio
Related Posts
- Advertisement -









No comments yet.