አሜሪካ ለመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የ8.6 ቢሊዮን ዶላር የጦር መሳሪያ ሽያጭ አፀደቀች

- Advertisement -
Sidebar AD

የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለታቀዱት የጦር መሳሪያ ሽያጮች የኮንግረሱን ግምገማ በድንገተኛ ሁኔታ በማለፍ፣ ለእስራኤል፣ ለኳታር፣ ለተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና ለኩዌት የሚቀርብ በድምሩ 8.6 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ የጦር መሳሪያ ጥቅል ማጽደቁ ተገለጸ።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ሽያጩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ ሽያጩ በአስቸኳይ እንዲከናወን የሚያስገድድ “አስቸኳይ ሁኔታ” መፈጠሩን ገልጸዋል።

ይህ ውሳኔ የተላለፈው አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ የጀመሩት ጦርነት ዘጠነኛ ሳምንቱን በያዘበትና በ ቀጠናው ያለው ውጥረት በጨመረበት ወቅት ነው።

ይህ የአሜሪካ እርምጃ የመጣው ኢራን በአጎራባች ሀገራት ላይ የአየር ጥቃት መፈጸሟን ተከትሎ ሲሆን፣ በሌላ በኩል በአሜሪካ እና በኔቶ አጋሮች መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ መሄዱ ተስተውሏል።

ትራምፕ በጀርመኑ መራሄ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርዝ ላይ በሰነዘሩት ትችት ሳቢያ፣ አሜሪካ በጀርመን የሚገኘውን የሰራዊት ቁጥር ለመቀነስ መወሰኗ ውጥረቱን አባብሶታል።

የጀርመን መከላከያ ሚኒስትር ቦሪስ ፒስቶሪየስ በሰጡት ምላሽ፣ የአሜሪካ ውሳኔ የሚጠበቅ መሆኑን ገልጸው፣ “እኛ አውሮፓውያን ለራሳችን ደህንነት የበለጠ ኃላፊነት መውሰድ ይኖርብናል” ብለዋል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ይህ የተፋጠነ የጦር መሳሪያ ዝውውር “ለአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ጥቅም ሲባል” የተደረገ መሆኑን አጽንኦት ሰጥቷል። በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ጦርነት በአሜሪካ ላይ ብቻ 25 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማስከተሉን የፔንታጎን መረጃዎች ያመለክታሉ።



Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: