ሮይተርስ የዜና ወኪል የፓኪስታን ምንጮችን ጠቅሶ አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማስቆም የሚያስችል አንድ ገጽ የመግባቢያ ሰነድ ለመፈራረም መቃረባቸውን ዘገበ።
በስም ያልተጠቀሱት ምንጮቹ ለሮይተርስ “በቅርቡ እናፈራርማለን፤ በጣመ ተቃርበናል” ሲሉ ተናግረዋል።
አክሲዮስ በበኩሉ ዋይት ሐውስ ጦርነቱን ለማስቆም የሚያስቸል ሰነድ ላይ ለመፈራረም መቃረቡን እንደሚያምን ዘግቧል።
ሁለት የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ማናገሩን እንዲሁም በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ የተሰጣቸው ሁለት ሌሎች ምንጮችን የጠቀስው መገናኛ ብዙኃኑ የመግባቢያ ሰነዱን ሊፈረም መሆን አረጋግጠዋል።
ባለ አንድ ገጽ ነው የተባለው የመግባቢያ ሰነድ ስለ ኒውክሌር ድርድር ማዕቀፍን እንደሚያስቀምጥ ተጠቅሷል።
ከእነዚህም መካከል የኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም መቋረጥ፣ የማዕቀብ መነሳት እና በሆርሙዝ ወሽመጥ ያለ ምንም እክል መርከቦች እንዲንቀሳቀሱ ማድረግ በሰነዱ ላይ መካተታቸው ተዘግቧል።
በሁለቱ አገራት ንግግር ውስጥ የኒውክሌር ፕሮግራም መቋረጥ እና የሆርሙዝ ወሽመጥ ዳግም መከፈት ሳያግባቧቸው የቆዩ ጉዳዮች ናቸው።
አክሲዮስ ምንጮችን ጠቅሶ በርካቶቹ በሰነዱ ላይ የተጠቀሱት ነጥቦች የመጨረሻ ስምምነት እንዳልተደረሰባቸው ዘግቧል።
ዩናይትድ ስቴትስ በሚቀጥሉት 48 ሰዓታት ውሰጥ ከቴህራን ምላሽ ለማግኘት እየጠበቀች ሲሆን እስካሁን ምንም ዓይነት ስምምነት የተደረሰበት ነገር አለመኖሩን ምንጮችን ጠቅሶ አክሲዮስ ዘግቧል።

Source: Yeneta Tube








No comments yet.