#Ethiopia | የአውሮፓው ግዙፍ እና በዝቅተኛ የዋጋ ተመኑ የሚታወቀው ራያንኤር (Ryanair)፣ በበረራ ወቅት የሚፈጠሩ የረብሻ ድርጊቶችን ለመቀነስ በአውሮፕላን ማረፊያዎች ውስጥ የሚቀርብ የአልኮል ሽያጭ ላይ “የቆርጥ ቀን” ገደብ እንዲጣል ጥሪ አቀረበ።
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ማይክል ኦሊሪ፣ በአውሮፕላን ማረፊያዎች ውስጥ የሚታየውን “ያለ ገደብ መጠጣት” ክፉኛ ኮንነዋል። እንደ ኦሊሪ ገለፃ፣ ጉዳዩ አየር መንገዱን ለከፍተኛ ኪሳራና ለደህንነት ስጋት እየዳረገው ይገኛል።
አየር መንገዱ በዋናነት የሚከተሉት ህጎች እንዲተገበሩ እየጠየቀ ነው፡-
-ከጠዋቱ 4 ሰዓት (10 AM) በፊት በአየር ማረፊያ ቡና ቤቶችና ምግብ ቤቶች ውስጥ ማንኛውም አይነት የአልኮል ሽያጭ እንዲታገዱ።
-ለአንድ ተሳፋሪ ከሁለት መጠጥ በላይ እንዳይሸጥላቸው።
-ይህንን ገደብ ተግባራዊ ለማድረግ እያንዳንዱ ተሳፋሪ መጠጥ በሚገዛበት ወቅት የመሳይፈሪያ ትኬቱን (Boarding Pass) እንዲያሳይ በማድረግ ሽያጩን መቆጣጠር።
ማይክል ኦሊሪ እንደሚሉት፣ በቅርብ ጊዜያት በአልኮልና በተለያዩ አደንዛዥ እጾች ተፅዕኖ ስር ሆነው የበረራ ሰራተኞችን የሚያጠቁና ረብሻ የሚፈጥሩ ተሳፋሪዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል።
“በአሁኑ ወቅት በረብሻ ምክንያት በቀን በአማካይ አንድ በረራን አቋርጠን በተለዋጭ አየር ማረፊያ ለማሳረፍ እየተገደድን ነው” ሲሉ የችግሩን ስፋት ገልጸዋል።
ራያንኤር የአየር ማረፊያ አስተዳዳሪዎችንም ከመወረፍ አልተቆጠበም። አየር ማረፊያዎች የተሳፋሪዎችን ደህንነት ከማስጠበቅ ይልቅ፣ ከመጠጥ ሽያጭ የሚገኘውን ትርፍ ብቻ እያሳደዱ ነው ሲል ከሷል።
ይህ የራያንኤር አቋም በጉዞ ኢንዱስትሪው ውስጥ ትልቅ መነጋገሪያ የፈጠረ ሲሆን፣ ተሳፋሪዎች ከጉዞ በፊት ያላቸውን “የመዝናናት ነፃነት” እና የአየር መንገዱን “የደህንነት ስጋት” ያፋጠጠ ሆኗል።
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #
#Ryanair #AviationSafety #TravelNews #AirportRules #FlightSafety #MichaelOLeary #የጉዞ_ዜና
Source: GetuTemesgen









No comments yet.