ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ሊመጡ ነውየፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ ሊ…

- Advertisement -
Sidebar AD
ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ሊመጡ ነው
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ መሆኑ ተዘግቧል
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኬንያ ናይሮቢ የሚካሄደውን “አፍሪካ ፎርዋርድ” ጉባኤ ካጠናቀቁ በኋላ፣ በመጪው ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለአጭር የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ታውቋል።
ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡት በጥንቃቄ የተመረጡ የፈረንሳይ ግዙፍ ኩባንያዎች መሪዎችን በማስከተል ሲሆን፣ ጉብኝቱም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው ይላል የካፒታል ዘገባ።
በፕሬዝዳንቱ የታጀበው ልዑክ እንደ ካርፉር ያሉ ታዋቂ የችርቻሮ ንግድ ተቋማትን እና ሜሪዲያም የተሰኘውን የኢንቨስትመንት ድርጅት አመራሮችን ያካተተ ሲሆን፣ በተለይም ካርፉር ከኢትዮጵያው ሚድሮክ ጋር በፈጠረው የፍራንቻይዝ ስምምነት አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት ማቀዱ የጉብኝቱ አንዱ ዋነኛ ትኩረት መሆኑ ተጠቁሟል።
@seledadotio
@seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2