ማዛጋት ንቃተ-ህሊናን ይጨምራል ተባለ

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | ​ማዛጋት ለዘመናት የድካም ወይም የእንቅልፍ መምጣት ምልክት ተደርጎ ቢወሰድም፣ በአውስትራሊያው ሲድኒ ዩኒቨርስቲ የተደረገ አዲስ ጥናት ግን ማዛጋት ለአንጎል ጤና እና ለሰውነት ንቃት ወሳኝ መሆኑን ይፋ አድርጓል።

“የአንጎል ቅዝቃዜ” (Brain Cooling) በተሰኘው በዚህ ሳይንሳዊ ግኝት መሠረት፣ ስናዛጋ የምናስገባው ቀዝቃዛ አየርና የምናደርገው የፊት ጡንቻዎች እንቅስቃሴ የአንጎላችን ሙቀት እንዲቀንስ በማድረግ የላቀ የማሰብ ብቃት እንዲኖረው ይረዳል።

​ተመራማሪዎቹ እንደሚሉት ከሆነ፣ ማዛጋት በሰውነታችን ውስጥ ያለውን የንቃተ-ህሊና መጠን ከፍ የሚያደርግ እንደ ትልቅ “ሞተር” የሚያገለግል ሲሆን፣ አንጎል በተረጋጋ እና በቀዘቀዘ ስሜት ይበልጥ ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲሠራ ያግዘዋል።

ይህም ማዛጋት የተፈጥሮ አንዱና ዋነኛው ራስን የማነቂያና የመጠበቂያ መንገድ መሆኑን ያረጋግጣል።

Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#viaChannel1Tv ​#ጤና #ሳይንስ #ማዛጋት #አንጎል #ጤናማ_አኗኗር #ምርምር #ንቃት #HealthTips #ScienceNews #BrainHealth #Yawning #Ethiopia


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1