#FastMereja I የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ላደገው የነገሌ አርሲ እግር ኳስ ክለብ የ50 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ አደረገ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ክለቡ በሊጉ እያሳየ የሚገኘውን ውጤታማ ጉዞ ለማጠናከርና ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ ይህንን ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ መፍቀዳቸው ታውቋል።
ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ክለቡ የዞኑንና የክልሉን ስም በስፖርቱ ዓለም ለማስጠራት እያደረገ ላለው ጥረት እውቅና በመስጠት፣ ድጋፉ ለክለቡ ተጫዋቾችና አመራሮች ትልቅ መነሳሳትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
Source: FastMereja








No comments yet.