ጣሊያን ለቀበና ወንዝ ተፋሰስ ልማት የሚውል የ5 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ አደረገች

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | በአዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ የሚገኘውን የቀበና ወንዝ ተፋሰስ በዘላቂነት ለማልማት የሚያስችል የ5 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነት በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያና በጣሊያን መንግሥታት መካከል ተፈርሟል።

የቀበና ወንዝ ገባር ወንዞች ልማት ፕሮጀክት ተብሎ የተሰየመው ይህ ዕቅድ በአዲስ አበባ የውበትና የአረንጓዴ ልማት ቢሮ አማካኝነት ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናል።

የልማቱ ዋነኛ ግብ የወንዙን ተፈጥሯዊ ስነ ምህዳር መልሶ በማደስ የአካባቢውን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ገጽታ መቀየር ሲሆን ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ለምታደርገው ጥረት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ በከፍተኛ ሁኔታ የተበከሉ ሁለት ገባር ወንዞችን መልሶ ለማልማት ትኩረት ያደርጋል።

በሥራውም የፍሳሽ ማስወገጃ ግንባታዎችን ማከናወን፣ የጎርፍ መከላከያ ግንቦችን መገንባት፣ የወንዝ ዳርቻዎችን በዘመናዊ ጥበብ መጠበቅ እንዲሁም የአረንጓዴ መናፈሻዎችንና የሕዝብ አገልግሎት መስጫዎችን ማቋቋም ይካተታሉ።

ይህም የወንዝ ብክለትንና የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባለፈ ለነዋሪዎች ጽዱና ለጤና ተስማሚ የሆነ የመዝናኛ ስፍራ እንደሚፈጥር ታምኖበታል።

#የቀበናወንዝ #አረንጓዴልማት #ኢትዮጵያናጣሊያን #የአየርንብረትለውጥ #አዲስአበባ #ልማት
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa






Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: