የአሜሪካ የቻይና መኪናዎች እገዳ በአፍሪካ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ ላይ ተፅዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል ተጠቆመ
በአሜሪካ ምክር ቤት በሁለቱም የፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ የቀረበውና በቻይና የተሰሩ መኪናዎች እንዲሁም የመኪና መለዋወጫዎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የሚከለክለው አዲስ የህግ ረቂቅ፣ በአፍሪካ እያደገ ባለው የመኪና መገጣጠም ዘርፍ ላይ ከፍተኛ አንድምታ ሊኖረው እንደሚችል ተገለጸ።
የአሜሪካ የደህንነትና የኢኮኖሚ ስጋቶችን መሰረት ያደረገው ይህ እገዳ፣ የቻይና የመኪና አምራቾች ፊታቸውን በስፋት ወደ አፍሪካ ገበያ እንዲያዞሩና ምርቶቻቸውን ወደ አህጉሪቱ እንዲያፈሱ የሚያስገድድ እንደሆነ ተመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት አፍሪካ ከዓለም አቀፍ የመኪና ምርት ውስጥ የምታበረክተው ድርሻ ከሁለት በመቶ በታች ቢሆንም፣ እንደ ቢ.ዋይ.ዲ (BYD) እና ቼሪ (Chery) ያሉ የቻይና ኩባንያዎች በአህጉሪቱ ያላቸውን የተሽከርካሪ ሽያጭና የመገጣጠም አጋርነት በከፍተኛ ሁኔታ እያሰፉ ይገኛሉ።
ይህ የቻይና ኩባንያዎች ወደ አፍሪካ በስፋት መተምመም፣ እንደ ደቡብ አፍሪካ እና ሞሮኮ ያሉ ግዙፍ አምራቾችን ብቻ ሳይሆን እንደ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ኬንያ ያሉ የአገር ውስጥ መኪና መገጣጠም ኢንዱስትሪን ለማሳደግ የሚጥሩ ሀገራትን ፈተና ላይ ሊጥል እንደሚችል ተገምቷል።
በአሜሪካ ገበያ የተገደቡት ምርቶች ወደ አፍሪካ በብዛት መፍሰሳቸው ለአገር ውስጥ አነስተኛ መገጣጠሚያዎች የገበያ ፉክክርን የሚያከብድ ሲሆን፣ ይህም በአገር ውስጥ የሚመረቱ መኪናዎችን ተወዳዳሪነት ሊቀንስ እንደሚችል ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ።
@seledadotio
@seledadotio
በአሜሪካ ምክር ቤት በሁለቱም የፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ የቀረበውና በቻይና የተሰሩ መኪናዎች እንዲሁም የመኪና መለዋወጫዎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የሚከለክለው አዲስ የህግ ረቂቅ፣ በአፍሪካ እያደገ ባለው የመኪና መገጣጠም ዘርፍ ላይ ከፍተኛ አንድምታ ሊኖረው እንደሚችል ተገለጸ።
የአሜሪካ የደህንነትና የኢኮኖሚ ስጋቶችን መሰረት ያደረገው ይህ እገዳ፣ የቻይና የመኪና አምራቾች ፊታቸውን በስፋት ወደ አፍሪካ ገበያ እንዲያዞሩና ምርቶቻቸውን ወደ አህጉሪቱ እንዲያፈሱ የሚያስገድድ እንደሆነ ተመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት አፍሪካ ከዓለም አቀፍ የመኪና ምርት ውስጥ የምታበረክተው ድርሻ ከሁለት በመቶ በታች ቢሆንም፣ እንደ ቢ.ዋይ.ዲ (BYD) እና ቼሪ (Chery) ያሉ የቻይና ኩባንያዎች በአህጉሪቱ ያላቸውን የተሽከርካሪ ሽያጭና የመገጣጠም አጋርነት በከፍተኛ ሁኔታ እያሰፉ ይገኛሉ።
ይህ የቻይና ኩባንያዎች ወደ አፍሪካ በስፋት መተምመም፣ እንደ ደቡብ አፍሪካ እና ሞሮኮ ያሉ ግዙፍ አምራቾችን ብቻ ሳይሆን እንደ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ኬንያ ያሉ የአገር ውስጥ መኪና መገጣጠም ኢንዱስትሪን ለማሳደግ የሚጥሩ ሀገራትን ፈተና ላይ ሊጥል እንደሚችል ተገምቷል።
በአሜሪካ ገበያ የተገደቡት ምርቶች ወደ አፍሪካ በብዛት መፍሰሳቸው ለአገር ውስጥ አነስተኛ መገጣጠሚያዎች የገበያ ፉክክርን የሚያከብድ ሲሆን፣ ይህም በአገር ውስጥ የሚመረቱ መኪናዎችን ተወዳዳሪነት ሊቀንስ እንደሚችል ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ።
@seledadotio
@seledadotio









No comments yet.