በተቀጠረች በ3ኛው ሳምንት ከ200 መቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት ንብረት የሰረቀች የቤት ሰራተኛ በእስራት ተቀጣች።

- Advertisement -
Sidebar AD

ተከሳሽ ምስጋና ሙሉጌታ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመችው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ልዩ ቦታው ካራ ቆሬ መብራት ኃይል ጀርባ ከሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ነው።

ግለሰቧ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ስትሰራ ከነበረችበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ለ ሦስት ሳምንታት ስትሰራ ቆይታለች፡፡

አሰሪዎቿ ወደ ስራ በሄዱበት አጋጣሚ ግምታቸው 267ሺህ 340 ብር የሚያወጡ የተለያዩ የአዋቂና የህፃናት አልባሳትን፣ ታብሌት ስልክ፣ የጆሮና የጣት የወርቅ ጌጣጌጥ፣ የብር ሃብል፣ የእጅ ሰዓትና 3 ሺህ 500 ብር ሠርቃ ትሰወራለች፡፡

ተከሳሿ በወቅቱ ስትቀጠር በቂ ተያዥ ባታቀርብም ፖሊስ ባደረገው ክትትል ግለሰቧ ከነበረችበት ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠምባሮ ልዩ ወረዳ ከእነ ንብረቱ እንተያዘች በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የካራ አካበቢ ፖሊስ ጣቢያ አስታውቋል።

ፖሊስ በግለሰቧ ላይ አስፈላጊውን ምርመራ በማጣራት አቃቤ ህግ ክስ መስርቶባት ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ የወንጀል ችሎት ተከሳሽ ምስጋና ሙሉጌታ ጥፈተኛነቷን በማረጋገጡ በ5 አመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኗል፡፡

ህብረተሰቡ የቤት ሰራተኛ ሲቀጥር በቂ ተያዥና ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ያላቸው መሆኑን ማረጋገጥ እንዳለባቸው እና ወንጀል ተፈፅሞ ሲገኝም በወቅቱ ለፖሊስ ማሳወቅ እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል።

Addis Ababa police




Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: