የቻይና የእርዳታ እህል ኩባ ገብቷል

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | ቻይና ለከባድ የምግብና የኃይል ቀውስ ውስጥ ለምትገኘው ኩባ ቃል ከገባችው 60 ሺህ ቶን የአደጋ ጊዜ የምግብ ድጋፍ ውስጥ የመጀመሪያውን 15 ሺህ ቶን ሩዝ በሃቫና ወደብ በኩል አስረከበች።

​ይህ በቤጂንግ የተላከው ግዙፍ ጭነት በኩባ በቅርብ ታሪክ የተደረገ ትልቁ የምግብ ድጋፍ ሲሆን፥ በአሜሪካ ማዕቀብና ከቬንዙዌላ የሚመጣው ነዳጅ በመቋረጡ ምክንያት በደሴቲቱ ላይ የተከሰተውን ታይቶ የማይታወቅ የሸቀጦችና የኃይል እጥረት ለመቅረፍ ያለመ ነው።

​የኩባው ፕሬዝዳንት ሚጌል ዲያዝ-ካኔል ዕርዳታው በሁሉም ግዛቶች ለሚገኙ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ ለሆስፒታሎችና ለትምህርት ቤቶች እንደሚሰራጭ የገለጹ ሲሆን፥ በኩባ የቻይና አምባሳደር ሁዋ ሺን በበኩላቸው እርምጃው በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ አጋርነት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።

​#China #Cuba #Havana #FoodAid #Geopolitics #GlobalNews #ChinaCubaRelations


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1