የአረፋት ተራራ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ምዕመናንን ያስተናገደው ታላቁ የሐጅ የጸሎት ሥነ ሥርዓት ተከናወነ

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | ከዓለም ዙሪያ የተሰባሰቡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሳዑዲ አረቢያ ምዕራባዊ ክፍል በሚገኘው ታሪካዊው የአረፋት ተራራ ላይ በመገኘት የዘንድሮውን የ1447ኛው ዓመታዊ የሐጅ ጉዞ ዋነኛ የጸሎት ሥነ ሥርዓት አከናውነዋል።

ለስድስት ቀናት የሚዘልቀው ይህ ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ የእስልምና እምነት መሠረታዊ ምሰሶዎችን የሚያሳይ ሲሆን የነቢዩ ኢብራሂምና የቤተሰባቸውን ታሪካዊ የሕይወት ፈተናዎች ለማስታወስ የሚደረግ ነው።

በአሁኑ ወቅት ምዕመናኑ በአረፋት ተራራ ላይ በመሆን የዱዓ እና አጠር ያሉ የሰላት ሥነ ሥርዓቶችን እያከናወኑ ይገኛሉ።

ፀሐይ ስትጠልቅ ደግሞ የአላህን ስም እያወደሱ ወደ ሙዝዳሊፋ በመጓዝ የሌሊት ጸሎታቸውን የሚያደርጉ ሲሆን እዚያው በባዶ መሬት ላይ እስከ ንጋት ድረስ በታላቅ ትሕትና ያድራሉ።

ይህ ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ በአረፋት መቆምን፣ በሙዝደሊፋ ማደርን፣ በሚና ሰይጣን የሚወገዝበትን የጠጠር ውርወራ ማከናወንን እና በመካ በሚገኘው ታላቁ መስጊድ የካዕባ የስንብት ጠዋፍ ማድረግን ያጠቃልላል።

#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: