ለቃል መውረድ ለሥጋ ማረግ ምክንያት የሆነችው የእመቤታችን በአለ ንግስ በቃጥላ!
እንኳን ለደብረ ምጥማቅ በዓል አደረሳችሁ!
በደብረ ምጥማቅ ከግንቦት 21-25 እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ብርሃን ተጎናጽፋና በሠራዊተ መላእክት ታጅባ ተገልጣለች፤ በዚያን ጊዜም ሱራፌል ማዕጠንታቸውን ይዘው ሰገዱላት፤ እንዲህ እያሉም አመሰገኗት፤ ‹‹አብ በሰማይ አይቶ እንዳንቺ ያለ አላገኘም፤ ባንቺም ሰው ሆነ፡፡››(መጽሐፈ ስንክሳር ግንቦት ፳፩ ገጽ. ፫፻፲፰)
የተወደዳችሁ ኦርቶዶክሳውያን ግንቦት 21 የደብረ ምጥማቅን በዓል በቃጥላ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም በማሳለፍ ከበረከቷ ተካፋይ እንድትሆኑ በልዑል እግዚአብሔር ስም ተጋብዛችኋል፡፡
እመቤታችን የህይዎታቸውን ቋጠሮ የፈታችላቸው በእንባ ሲመሰክሩ ያያሉ። ይምጡ ፣ ጌታም ሸክማችሁ የከበዳችሁ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ እንዳለ።
የቤተክርሲያኒቱን የልማት ሥራዎች ለመደገፍ፡-
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000249446975
አባይ ባንክ አካውንት አካውንት ቁጥር 1641119233527011
Source: GetuTemesgen









No comments yet.