በአዲስ አበባ የሚገኙ አንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች በዲጂታል የተመዘገቡ መራጮችን ስም ዝርዝር በማኑዋል (በወረቀት) እያመሳከሩ በማሳለፍ ላይ በመሆናቸው ምክንያት ከፍተኛ መስተጓጎል እና የእንግልት ሰልፍ መፈጠሩ ተነገረ። ከንጋቱ 12 ሰዓት ጀምረው ድምፅ ለመስጠት የተሰለፉ ዜጎች በአንድ አስመራጭ ብቻ በመስተናገዳቸው ሳቢያ ለሰዓታት ለመቆም መገደዳቸውንና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጣቸው በምሬት እየጠየቁ ይገኛሉ።



Source: FastMereja









No comments yet.