የምርጫ ቦርድ በሰልፍ ላይ ለሚገኙ መራጮች የድምፅ መስጫ ሰዓት መራዘሙን ገለጸ

- Advertisement -
Sidebar AD

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዕለቱ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ማብቂያ እስከሆነው 12:00 ሰዓት ድረስ በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው በሰልፍ ላይ የነበሩ መራጮች በሙሉ ድምፅ ሰጥተው እስኪያጠናቅቁ ድረስ ሂደቱ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

ይህ ውሳኔ የተላለፈው በምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 4 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ሲሆን፣ ቦርዱ አስገዳጅ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ የድምፅ መስጫ ሰዓትን ማራዘም እንደሚችል በሕጉ ላይ ተደንግጓል።

ውሳኔው የወጣው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ነው።


Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: