የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዕለቱ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ማብቂያ እስከሆነው 12:00 ሰዓት ድረስ በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው በሰልፍ ላይ የነበሩ መራጮች በሙሉ ድምፅ ሰጥተው እስኪያጠናቅቁ ድረስ ሂደቱ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው በምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 4 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ሲሆን፣ ቦርዱ አስገዳጅ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ የድምፅ መስጫ ሰዓትን ማራዘም እንደሚችል በሕጉ ላይ ተደንግጓል።
ውሳኔው የወጣው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ነው።
Source: Yeneta Tube









No comments yet.