ቻይና ግዙፍ የዳታ ማዕከላትን በባህር ወለል ስር ማሰማራት ጀመረች፤ ባህሩ እንደ ተፈጥሯዊ ማቀዝቀዣ ያገለግላል! የቴክኖሎጂው …

- Advertisement -
Sidebar AD
🔴 ቻይና ግዙፍ የዳታ ማዕከላትን በባህር ወለል ስር ማሰማራት ጀመረች፤ ባህሩ እንደ ተፈጥሯዊ ማቀዝቀዣ ያገለግላል!
የቴክኖሎጂው ልዕለ-ኃያል ቻይና የዓለማችንን የዲጂታል መሠረተ-ልማት አወቃቀር ሙሉ በሙሉ ሊቀይር የሚችል እጅግ አስደናቂ የፈጠራ ስራ በተግባር ማከናወን መጀመሯ ይፋ ሆኗል። ሀገሪቱ እጅግ ግዙፍ የሆኑ የዳታ ማዕከላትን (Data Centers) በቀጥታ በውቅያኖስ ወለል ላይ የማስቀመጥ እና ለንግድ አገልግሎት የማዋል ስራን በተሳካ ሁኔታ ጀምራለች።
ይህ ታይቶ የማይታወቅ አዲስ አሰራር የዳታ ማዕከላቱ ሰርቨሮች መረጃዎችን በከፍተኛ ፍጥነት በሚያሰሉበት ጊዜ የሚፈጥሩትን እጅግ ኃይለኛ ሙቀት ለማስወገድ ቀዝቃዛውን የባህር ውሃ እንደ ተፈጥሯዊ ማቀዝቀዣ የሚጠቀም ነው። ይህም በየብስ ላይ እንደሚደረገው ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ማቀዝቀዣ ማሽኖችን (Chillers) የመጠቀም አስፈላጊነትን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል።
ይህ የቴክኖሎጂ ስኬት ባህላዊ የዳታ ማዕከላት የሚጠይቁትን የኤሌክትሪክ ፍጆታ በ22.8 በመቶ የሚቀንስ ሲሆን፣ ለባህላዊ ማቀዝቀዣ የሚባክነውን በሚሊዮን የሚቆጠር ሊትር ንጹህ የውሃ ፍጆታን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል። በተጨማሪም በየብስ ላይ ሊያዝ የሚችለውን ውድ የቦታ ስፋት በ90 በመቶ መታደግ ያስቻለ ሲሆን፣ ማዕከላቱ በቀጥታ በባህር ላይ ከተተከሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ጋር የተገናኙ በመሆኑ ሙሉ በሙሉ በአረንጓዴ እና ታዳሽ ኃይል የሚሰሩ ናቸው።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1