በቤት ጣራ ላይ ሶላር ፓኔል እንዲገጠም የሚያስገድድ መመሪያ ተዘጋጀለጊዜው የሚተገበረው አዲስ በሚገነቡ ቤቶች ላይ ነው ተብሏል።…

- Advertisement -
Sidebar AD
በቤት ጣራ ላይ ሶላር ፓኔል እንዲገጠም የሚያስገድድ መመሪያ ተዘጋጀ
ለጊዜው የሚተገበረው አዲስ በሚገነቡ ቤቶች ላይ ነው ተብሏል።
አዲስ የመኖሪያ ቤቶችና ሕንፃዎችን በሚገነቡበት ወቅት በጣሪያቸው ላይ የሶላር ፓኔል ቴክኖሎጂን እንዲገጥሙ የሚያደርግ አዲስ ብሔራዊ መመሪያ መዘጋጀቱን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ከመጪው ሰኔ 30 ቀን ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይህ መመሪያ፣ በሀገሪቱ ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት በታዳሽ ኃይል ለመተካት ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ሕጉ ለጊዜው አስገዳጅ ባይሆንም የመጀመሪያ ምዕራፍ ትግበራው በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚጀመር ተገልጿል።
የሶላር ቴክኖሎጂዎች ዋጋ ከፍተኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞም፣ የመግዛት አቅም ለሌላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ልዩ ልዩ ማበረታቻዎች እንደሚዘጋጁ ሚኒስቴሩ አመልክቷል።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2