ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን  ጋር የተፈጠረው ግጭት ማክተሙንና ታሪካዊ ስምምነት ላይ መደረሱን አስታወቁ ትራምፕ ለሴኔት እጩ ባሪ ሙ…

- Advertisement -
Sidebar AD
ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን  ጋር የተፈጠረው ግጭት ማክተሙንና ታሪካዊ ስምምነት ላይ መደረሱን አስታወቁ
ትራምፕ ለሴኔት እጩ ባሪ ሙር በተዘጋጀ የድጋፍ መድረክ ላይ እንደተናገሩት፣ ስምምነቱ ዋሽንግተን የጠየቀቻቸውን ነጥቦች በሙሉ ያካተተ ነው።
​በዚህም መሰረት ቴህራን የኑክሌር መሣሪያን በጭራሽ ላለማልማትና ላለመግዛት ተስማምታለች።
ስምምነቱ ሲፈረምም ስትራቴጂካዊው የሆርሙዝ ሰርጥ  በይፋ ክፍት እንደሚሆንና የአሜሪካ ወታደሮች ወደ ሀገራቸው እንደሚመለሱ ተገልጿል።
ስምምነቱ በሳምንቱ መጨረሻ በአውሮፓ ምድር በምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ፊት ሊፈረም እንደሚችል ይጠበቃል።
​ሆኖም ዋሽንግተን ይህንን እንደ ታላቅ የዲፕሎማሲ ድል ብታቀርበውም፣ ከኢራን በኩል እስካሁን ይፋዊ ማረጋገጫ አልተሰጠም።
  ስምምነቱ የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁንም ጭምር ያስገረመ መሆኑ ተገልጿል።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: