ኢሎን ማስክ የስፔስ ኤክስ አክሲዮን ማደጉን ተከትሎ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊየነር ሆነአርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም የስ…

- Advertisement -
Sidebar AD
ኢሎን ማስክ የስፔስ ኤክስ አክሲዮን ማደጉን ተከትሎ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊየነር ሆነ
አርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም የስፔስ ኤክስ (SpaceX) አክሲዮኖች በናስዳቅ የገበያ ማዕከል ለመጀመሪያ ጊዜ ለሕዝብ ክፍት በሆኑበት ዕለት የ11 በመቶ ዕድገት በማሳየት 150 ዶላር ደርሰዋል።
ይህ በታሪክ ትልቁ የሆነው የአክሲዮን ሽያጭ (IPO) የኩባንያውን አጠቃላይ የገበያ ዋጋ 2 ትሪሊዮን ዶላር ያደረሰው ሲሆን፣ ባለቤቱን ኢሎን ማስክን የዓለማችን የመጀመሪያው ባለ ትሪሊዮን ዶላር (Trillionaire) ሀብታም አድርጎታል።
ከ75 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ያስገኘው ይህ ሽያጭ፣ ኩባንያውን ከቴስላ እና ሜታ በላይ እንዲሰለፍ አድርጎታል።
እ.ኤ.አ በ2002 የተመሠረተው ስፔስ ኤክስ፣ አሁን ላይ የሳተላይት አገልግሎትን፣ የኤአይ (xAI) ኩባንያን እና የኤክስ (X) ማህበራዊ ሚዲያን ያካተተ ግዙፍ ጥምረት ሆኗል።
ማስክ በሰጠው መግለጫ የኩባንያው ቀጣይ ግብ የሰውን ልጅ ወደ ጨረቃና ማርስ ማድረስ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2