ወላይታ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ ​ከወላይታ ሶዶ ወደ ገሳ ከተማ 50 ሰዎችን አሳ…

- Advertisement -
Sidebar AD
ወላይታ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ
​ከወላይታ ሶዶ ወደ ገሳ ከተማ 50 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ “ዛሮ ቁልቁለት” ኤልፋ በተባለ አስቸጋሪ መንገድ ላይ ተገልብጧል።
በአደጋው የ4 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ያለፈ ሲሆን፣ በ22 ሰዎች ላይ ከባድ እና በ24 ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።
​የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን እንደገለፀው፣ ተጎጂዎች ወደ ህክምና ተቋማት ተወስደዋል።
ይሁን እንጂ በደረሰው የጉዳት መጠን ምክንያት የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተገልፇል።
​የአካባቢው አስቸጋሪ መልክዓ ምድር ለክስተቱ መንስኤ ሳይሆን እንዳልቀረ የተጠቆመ ሲሆን፣ ፖሊስ ስለ አደጋው ዝርዝር ምርመራ እያደረገ ይገኛል።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2