በባሕር ዳር ለተወዳጁ ሰማኸኝ በለው መንገድ ተሰየመለት!!

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ለጎጃም ግሽ አባይ የኪነት ቡድን አባል ለነበረው በኢትዮጵያውያን ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ላተረፈው ለአርቲስት ሰማህኝ በለው መንገድ በስሙ ሰይሟል::

ይህ የታወቀው ዛሬ የባሕር ዳር ህዝብ ለአርቲስቱ መታሰቢያ ባዘጋጀበት ሲሆን ከባሕር ዳር ልማት ባንክ እሰከ አዲሱ ስቴዲየም ያለው መንገድ “ሰማኸን በለው መንገድ” ተብሎ እዲጠራ መወሰኑን የከተማዋ ከንቲባ ጎሹ አሳውቀዋል::

አርቲስት ሰማኸኝ በለው በባሕርዳር ተወልዶ እጅግ የተዋጣለት የባህል ዘፍሮችን ማበርክት የቻለና ህይወቱን በሙሉ በሙዚቃ ስራ ላይ ያሳለፈ ተወዳጅ አርቲስት ነበረ::

በባሕር ዳር ለአርቲስቱ መታሰቢያ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችና ውሳኔዎች የሚቀጥሉ መሆናቸውንም መረጃዎች ያሳያሉ::

credit : ዘሐበሻ

Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)

#getutemesgen #getu


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1