«አእምሮዬ አካሌን ‘ደክሞሃል’ ብሎ እንዲያዝዘው አልፈቅድለትም»

- Advertisement -
Sidebar AD

ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ

#Ethiopia | ​የሳችሞ ማዕከል ፕሪስቲጅ አዲስ ጋር በመተባበር አንጋፋውን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ደጋግሞ ያሸነፈውን ኢትዮጵያዊ የረጅም ርቀት ተወዳዳሪ ሻምፒዮን ኃይሌ ገብረሥላሴን በመጋበዝ በስፖርት፣ በዲሲፕሊን እና ድንቅ ብቃትን በማውጣት ዙሪያ የሚያጠነጥን ልዩ የውይይት መድረክ ተዘጋጀ።

በሩጫ ታሪኩ ሁለት የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያዎችን ማሸነፍ የቻለውና የማራቶንን ጨምሮ 27 የዓለም ክብረወሰኖችን የሰባበረው ሀይሌ፣ ለስኬቱ ማማ ያበቃውን የስነ-ልቦና ጥንካሬ ለታዳሚው አካፍሏል።

​በውይይቱም ላይ በማለት ጠንካራ ቁርጠኝነትን ያሳየው ሀይሌ፣ እውነተኛ ታላቅነት ላይ ለመድረስ በአንድ ዓላማ ላይ ብቻ ማተኮር እንደሚገባ መክሯል። አክሎም «የመጀመሪያውና ዋናው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ክብረወሰንን መስበርና ማሸነፍ እንጂ ገንዘብ አይደለም» ሲል የስኬቱን ሚስጥር ገልጧል።

​ይህ በሳችሞ ማዕከል የተዘጋጀው ዝግጅት አሜሪካ የ2028ቱን የሎስ አንጀለስ ኦሎምፒክ ያሉ ታላላቅ ዓለም አቀፍ የስፖርት ኩነቶችን ለማስተናገድ በምትዘጋጅበት ወቅት የተካሄደ በመሆኑ፣ የሻምፒዮኑ የህይወት ተሞክሮ በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ስኬታማ ለመሆን ምን ያህል ትጋትና ራስን መስጠት እንደሚያስፈልግ ትልቅ ማሳያ ሆኖ ያገለግላል።

credit : የአሜሪካ ኤንባሲ በአዲስ አበባ

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)

#getutemesgen #getu


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2