#Ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ባካሄደው ስብሰባ፣ በላቀ የትምህርትና የምርምር አፈጻጸማቸው አንቱታን ያተረፉ ስምንት ምሁራንን ከተባባሪ ፕሮፌሰርነት ወደ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ማሳደጉን አስታወቀ።
ይህ ከፍተኛ የአካዳሚክ ማዕረግ ዕድገት የተሰጣቸው
👉 ዶ/ር በውቀቱ መሐሪ፣
👉 ዶ/ር ሞላ ተፈራ፣
👉 ዶ/ር ምሳዬ ሙላቴ፣
👉 ዶ/ር ጌትነት ማስረሻ፣
👉 ዶ/ር ደሴ ጥበበ፣
👉 ዶ/ር ማስተዋል ብርሀን፣
👉 ዶ/ር አስማማው አጥናፉ እና
👉 ዶ/ር አስማማው ዓለሙ ናቸው።
የተሰጠው የዕድገት ማዕረግ በአዲሱ የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ መሠረት የተከናወነ ሲሆን፣ ምሁራኑ በምርምር ሥራዎቻቸው፣ በማስተማር ሒደትና በተቋማዊ አመራር ላበረከቱት ጉልህና ከፍተኛ አስተዋጽኦ እውቅና የሰጠ ነው።
#ጎንደርዩኒቨርስቲ
#ጌጡተመስገን #ሚዲያናኮሚኒኬሽን
#Getutemesgen #Mediacommunication



Source: GetuTemesgen









No comments yet.