የአውሮፓ ሕብረት ተደጋጋሚ መግለጫ ስለ ትግራይና ስለ ህወሓት የአውሮፓ ሕብረት በኢትዮጵያ ልዑክ በሰሜን ኢትዮጵያ በተለይም በት…

- Advertisement -
Sidebar AD
የአውሮፓ ሕብረት ተደጋጋሚ መግለጫ ስለ ትግራይና ስለ ህወሓት 
የአውሮፓ ሕብረት በኢትዮጵያ ልዑክ በሰሜን ኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ ክልል እየታየ ባለው ወቅታዊ ውጥረት ላይ ያለውን ከፍተኛ ስጋት ገልጿል። 
ሕብረቱ ባወጣው መግለጫ መሠረት የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በቅርቡ የወሰዳቸውን እርምጃዎች ማለትም ትይዩ የሆነ የክልል ምክር ቤት ማቋቋሙንና በክልሉ ውስጥ በአንድ ወገን የሚደረገውን የውትድርና ምልመላ በጥብቅ ኮንኗል። 
እነዚህ ተግባራት እ.ኤ.አ በ2022 በፕሪቶሪያ የተፈረመውን ዘላቂ ግጭት ማቆም ስምምነት ደንቦችንና ግዴታዎችን በግልጽ የሚጥሱ መሆናቸውን ልዑኩ አስገንዝቧል። 
ስምምነቱ ወደ ነበረበት እንዲመለስና በተግባር ላይ እንዲውል ሁሉም ወገኖች አስቸኳይ ውይይት እንዲጀምሩ ጠይቋል። 
የአፍሪካ ሕብረት ከፍተኛ ተወካይ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ በክልሉ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚያደርጉትን የሽምግልና ጥረት ሕብረቱ ሙሉ በሙሉ እንደሚደግፍም አስታውቋል።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: