የትራምፕ ቡድን በኢራንና በሊባኖስ ጉዳይ ተከፋፍሏል

- Advertisement -
Sidebar AD

ቫንስ ከሩቢዮ ጋር በኢራን እና ሊባኖስ ጉዳይ ተከፋፍለዋል ተባለ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የደረሱበትን የመግባቢያ ሰነድ በተመለከተ በውስጥ እና በውጭ ትችት እየተሰነዘረበት ባለበት ወቅት የአሜሪካዉ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ ስምምነቱን በይፋ ለመከላከል በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ቀርበዋል።

ቫንስ በስዊዘርላንድ የተካሄዱትን ከኢራን ጋር ድርድሮች መርተው እንደነበር በመግለጽ የመግባቢያ ሰነዱ ጥሩ እመርታ መሆኑንና ለመጨረሻ ስምምነት ጠንካራ መሠረት መጣሉን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ቫንስ እስራኤል በስምምነቱ ላይ ያቀረበችውን ተቃውሞ በጥብቅ በመተቸት ዘጠኝ ሚሊየን ሕዝብ ያላት ሀገር ሁሉንም የብሔራዊ ደኅንነት ችግሮቿን በግድያ ብቻ መፍታት አትችልም ብለዋል።

በሌላ በኩል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ እስራኤልን በይፋ ከመተቸት ተቆጥበው ትኩረታቸውን በኢራን መንግሥት ላይ አድርገዋል።

ስለ ቫንስ አስተያየት በተጠየቁ ጊዜም ቀጥተኛ መልስ ከመስጠት ይልቅ ሄዝቦላህ በሳምንቱ መጀመሪያ በእስራኤል የፍተሻ ጣቢያ ላይ ስለፈጸመው ጥቃት አንስተዋል።

ይሁን እንጂ የኋይት ሀውስ ኃላፊዎች በቫንስና በሩቢዮ መካከል የፖሊሲ ክፍፍል እንዳለ የሚነሱትን ወሬዎች በማስተባበል ሁለቱም በአስፈላጊ የውጭ ጉዳይ ጉዳዮች ላይ በአንድነት እየሠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

Ethio Fm



Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: