“የነዳጅ ዋጋን በአስቸኳይ ቀንሱ!”፤ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በነዳጅ አከፋፋዮችና ማደያዎች ላይ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ አስተላለፉ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሀገሪቱ የሚገኙ የነዳጅ ችርቻሮ ነጋዴዎችና ማደያዎች የሚሸጡትን የነዳጅ ዋጋ በአስቸኳይ እና ያለምንም መዘግየት እንዲቀንሱ ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት ይፋዊ መልእክት፤ በአሁኑ ወቅት አንድ ባሬል ድፍድፍ ዘይት በዓለም ገበያ በ68 ዶላር አካባቢ እየተሸጠ ባለበትና የገበያው አቅጣጫም ወደ ታች እያቆለቆለ በሚገኝበት ሁኔታ ላይ፣ ቸርቻሪዎች የሚያስከፍሉት ዋጋ እጅግ በጣም ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም ነጋዴዎቹ ለዚህ መግለጫ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ትክክለኛውን ነገር ማድረግ እንዳለባቸው ያሳሰቡት ፕሬዝዳንት ትራምፕ፤ “ለታላቁ የአሜሪካ ሕዝብ ስትሉ ዋጋችሁን በአስቸኳይ ቀንሱ!” በማለት ትዕዛዝ ሰጥተዋል። ከትእዛዙ ጋር በተያያዘም ፍጹም ሕገ-ወጥ የሆነውንና ሕዝብን በዋጋ ጭማሪ መበዝበዝ የሚባለውን አሠራር እንደማይታገሡትና ቸርቻሪዎቹ ይህንን ትእዛዝ ካልፈጸሙ ወደፊት ትልቅና ከባድ ችግር እንደሚጠብቃቸው አስጠንቅቀዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ በሀገሪቱ የአንድ ጋሎን ነዳጅ ዋጋ 2 ዶላር ከ50 ሳንቲም አካባቢን ኢላማ በማድረግ እንዲቀነስ የጠየቁ ሲሆን፣ ይህም የዜጎችን የኑሮ ውድነት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያቃልል አስገንዝበዋል።
በተያያዘም ፕሬዝዳንቱ በከፍተኛ ታክስ ምክንያት የነዳጅ ዋጋ ሰማይ በነካባት የካሊፎርኒያ ግዛት ላይ ያላቸውን ከባድ ቅሬታ ሰንዝረዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሀገሪቱ የሚገኙ የነዳጅ ችርቻሮ ነጋዴዎችና ማደያዎች የሚሸጡትን የነዳጅ ዋጋ በአስቸኳይ እና ያለምንም መዘግየት እንዲቀንሱ ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት ይፋዊ መልእክት፤ በአሁኑ ወቅት አንድ ባሬል ድፍድፍ ዘይት በዓለም ገበያ በ68 ዶላር አካባቢ እየተሸጠ ባለበትና የገበያው አቅጣጫም ወደ ታች እያቆለቆለ በሚገኝበት ሁኔታ ላይ፣ ቸርቻሪዎች የሚያስከፍሉት ዋጋ እጅግ በጣም ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም ነጋዴዎቹ ለዚህ መግለጫ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ትክክለኛውን ነገር ማድረግ እንዳለባቸው ያሳሰቡት ፕሬዝዳንት ትራምፕ፤ “ለታላቁ የአሜሪካ ሕዝብ ስትሉ ዋጋችሁን በአስቸኳይ ቀንሱ!” በማለት ትዕዛዝ ሰጥተዋል። ከትእዛዙ ጋር በተያያዘም ፍጹም ሕገ-ወጥ የሆነውንና ሕዝብን በዋጋ ጭማሪ መበዝበዝ የሚባለውን አሠራር እንደማይታገሡትና ቸርቻሪዎቹ ይህንን ትእዛዝ ካልፈጸሙ ወደፊት ትልቅና ከባድ ችግር እንደሚጠብቃቸው አስጠንቅቀዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ በሀገሪቱ የአንድ ጋሎን ነዳጅ ዋጋ 2 ዶላር ከ50 ሳንቲም አካባቢን ኢላማ በማድረግ እንዲቀነስ የጠየቁ ሲሆን፣ ይህም የዜጎችን የኑሮ ውድነት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያቃልል አስገንዝበዋል።
በተያያዘም ፕሬዝዳንቱ በከፍተኛ ታክስ ምክንያት የነዳጅ ዋጋ ሰማይ በነካባት የካሊፎርኒያ ግዛት ላይ ያላቸውን ከባድ ቅሬታ ሰንዝረዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio









No comments yet.