የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሊዮን በረራ ጀመረ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፈረንይ ሊዮን ከተማ የመንገደኞች በረራ አገልግሎት ማስጀመሩን ይፋ አድርጓል።
ይህም ለአየር መንገዱ በፈረንሳይ 3ኛ፣ በአውሮፓ 23ኛ እንዲሁም የዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን ቁጥር 146 የሚያደርሰው መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በወቅቱ እንዳሉት፤ የበረራ አገልግሎቱ መጀመር አየር መንገዱ አፍሪካን ከዓለም ጋር የማገናኘት ጉዞው ተጨማሪ ስኬት ነው።
ወደ ሊዮን የጀመረው በረራ ለዓለም አቀፍ ተጓዦች ተጨማሪ ዕድል የሚፈጥር ስለመሆኑም አብራርተዋል፡፡
መንገደኞችን ከማመላለስ ባሻገር የሀገራት ሁለንተናዊ ትስስሮች እንዲጠናከሩ አቅም መፍጠር እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡
@Seledadotio
@Seledadotio
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፈረንይ ሊዮን ከተማ የመንገደኞች በረራ አገልግሎት ማስጀመሩን ይፋ አድርጓል።
ይህም ለአየር መንገዱ በፈረንሳይ 3ኛ፣ በአውሮፓ 23ኛ እንዲሁም የዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን ቁጥር 146 የሚያደርሰው መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በወቅቱ እንዳሉት፤ የበረራ አገልግሎቱ መጀመር አየር መንገዱ አፍሪካን ከዓለም ጋር የማገናኘት ጉዞው ተጨማሪ ስኬት ነው።
ወደ ሊዮን የጀመረው በረራ ለዓለም አቀፍ ተጓዦች ተጨማሪ ዕድል የሚፈጥር ስለመሆኑም አብራርተዋል፡፡
መንገደኞችን ከማመላለስ ባሻገር የሀገራት ሁለንተናዊ ትስስሮች እንዲጠናከሩ አቅም መፍጠር እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡
@Seledadotio
@Seledadotio









No comments yet.