በሰነዶች ማረጋገጫ ንብረት ገዝተው ስም ያላዛወሩ ዜጎች በአስቸኳይ ይዞታቸውን እንዲያስመዘግቡ ተጠየቀ ቀደም ባሉ ጊዜያት ከሪል …

- Advertisement -
Sidebar AD
በሰነዶች ማረጋገጫ ንብረት ገዝተው ስም ያላዛወሩ ዜጎች በአስቸኳይ ይዞታቸውን እንዲያስመዘግቡ ተጠየቀ
 
ቀደም ባሉ ጊዜያት ከሪል እስቴት አልሚዎችም ሆነ ከግለሰቦች ጋር የቤት ወይም የመሬት ግብይት ፈጽመው፣ በሰነዶች ማረጋገጫ ብቻ የያዙና እስካሁን የስመ-ንብረት ዝውውር ያላደረጉ አካላት በአስቸኳይ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ  ጥሪ ቀረበ ።
 
የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ መኮንን ያኢ እንደገለጹት፤ ግዢ ፈጽመው የስም ዝውውር ያላደረጉ ወገኖች ለከፍተኛ ጉዳትና ለአደጋ እየተጋለጡ ይገኛሉ።
 
የስመ-ንብረት ዝውውር ዋና ዓላማ አንድ ግለሰብ ያፈራውን ንብረት ለሌላ አካል የሚያስተላልፍበት ሕጋዊ ሥርዓት መሆኑንና የመጨረሻው መዳረሻም የይዞታ ማረጋገጫ (ካርታ) ማግኘት መሆኑን ኃላፊው አስረድተዋል።
 
በመሆኑም ባለንብረቶች መብታቸውን ለማስከበርና ንብረታቸውን ከማንኛውም ሕጋዊ ስጋት ለመጠበቅ ሲሉ፣ ሳይዘገዩ ወደ መሬት ተቋማት በመቅረብ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪ አቅርቧል።
 
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1