‎መቐለ ዩኒቨርሲቲ ከ2,900 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ

- Advertisement -
Sidebar AD


‎#Ethiopia | ​የመቐለ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 2,931 ተማሪዎችን በዛሬው እለት አስመርቋል።

‎የትምህርት ገበታቸውን በስኬት አጠናቀው ለምረቃ ከበቁት የዘንድሮ ተመራቂዎች መካከል 849ኙ ሴቶች መሆናቸው
‎በምረቃው መርሐግብር ላይ ተገልጿል።

‎​ዩኒቨርሲቲውን በዘንድሮ አመት 1,864 ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም 45 ዓለም አቀፍ ተማሪዎችን ጨምሮ 939 ተማሪዎችን በሁለተኛ ዲግሪ አስመርቋል።

‎ከተመራቂዎቹ ውስጥ 45 ተማሪዎች በሦስተኛ ዲግሪ (ፒኤችዲ) ሲሆኑ 83 የሚሆኑት ደግሞ በስፔሻሊቲ አጠናቀዋል።

‎​በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፋና ሓጎስ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር የትምህርት ጥራትን ይበልጥ ለማረጋገጥ እና የተመራቂዎችን የፈጠራ ክህሎት ለማሳደግ የሚያስችል ሰፊ የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ መደረጉን ጠቁመው፣ ተመራቂዎቹ በተሰማሩበት የሥራ መስክ ኅብረተሰቡን በቅንነትና በትጋት እንዲያገለግሉ አሳስበዋል።

‎Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)

‎#getutemesgen #getu #ጌጡ

​#MekelleUniversity ​#Graduation​#EthiopianUniversities​#HigherEducation






Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: