80 ቢሊዮን ዶላር ለዩክሬን

- Advertisement -
Sidebar AD

የአውሮፓ አባል ሀገራት ለዩክሬን 80 ቢሊዮን ዶላር የጦር ድጋፍ ሊያደርጉ ነው።

#Ethiopia | ሀገራቱ በየዓመቱ 70 ቢሊዮን ዩሮ (ወደ 80 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ) ወታደራዊ ድጋፍ ሊያደርጉ መሆኑ ታውቋል።

ይህ ድጋፍ ለሁለት ዓመታት (2026 እና 2027) የሚቀጥል ይሆናል ነው የተባለው።

ይህ ድጋፍ ዩክሬን እስከ 2027 መጨረሻ ድረስ ወታደራዊ አቅሟን እንድታሳድግ ለማስቻል ያለመ ነው ።

የተመደበው 80 ቢሊዮን ዶላር አዲስ የተመደበ ገንዘብ ብቻ ሳይሆን ቀደም ሲል በአውሮፓ ህብረት የተፈቀደው የብድር ድጋፍ እና የአባል ሀገራት የሁለትዮሽ የጦር መሳሪያ ድጋፎችን ያካተተ ነው።

በሐምሌ 7 እና 8 በአንካራ በሚካሄደው ጉባኤ ላይ ሩሲያ ለአውሮፓ እና አትላንቲክ ቀጠና ደህንነት ስጋት መሆኗ በይፋ ያውጃሉ ተብሏል።

ይህ ስምምነት በተለይ የአሜሪካ የፖለቲካ አቅጣጫዎች በሚቀያየሩበት ወቅት መደረጉ አውሮፓውያን ለዩክሬን ያላቸውን ድጋፍ በራሳቸው አቅም የመምራት ፍላጎት እንዳላቸው አቅማቸውን የሚያሳዩበት ይሆናል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል።

ሔኖክ ወ/ገብርኤል

#Ethiopia #GetuTemesgen #GetuNews
#Nato #Ankara #Ukraine
#AnnualsupportUkraine


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: