ቪኒሲየስ ጁኒየር ወደ አርሰናል?፦ አርሰናል የሪያል ማድሪዱን ኮከብ ለማስፈርም እንቅስቃሴ መጀመሩ ተሰማ

- Advertisement -
Sidebar AD

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮኑ አርሰናል በግራ መስመር የፊት ማጥቃት ክፍሉን ይበልጥ ለማጠናከር የብራዚልና የሪያል ማድሪድ ኮከብ የሆነውን ቪኒሲየስ ጁኒየርን ወደ ኤሚሬትስ ለማምጣት እንቅስቃሴ መጀመሩ ተዘገበ።

እንደ ዘገባዎች ገለጻ በክሉቦች መካከል እስካሁን ምንም ዓይነት ይፋዊ ግንኙነት ያልተደረገ ቢሆንም፣ የአርሰናል ፍላጎት ግን እውነተኛ ነው። የ2024 የባሎንዶር ዕጩ የ26 ዓመቱ የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች በሪያል ማድሪድ የማጠናቀቂያ የኮንትራት ዓመቱ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ አዲስ ስምምነት ላይ መድረስ ካልተቻለ ማድሪዶች ተጫዋቹን በሚቀጥለው ክረምት በነጻ ከማጣት ይልቅ አሁን ለመሸጥ ሊገደዱ ይችላሉ።

አርሰናል በዚህ የዝውውር መስኮት ሊያዛቸው ከቀረጻቸው የፊት መስመር ተጫዋቾች መካከል ጁሊያን አልቫሬዝ፣ ያን ዲዮማንዴ እና ብራድሊ ባርኮላ የሚገኙበት ሲሆን፣ የቪኒሲየስ ዝውውር ከተሳካ ግን ለኤሚሬትሱ ቡድን ትልቅና አስደናቂ ማጠናከሪያ ይሆናል።

የመድፈኞቹ አሰልጣኝ ስብስብ በዚህ የበጋ የዝውውር መስኮት ሊያንድሮ ትሮሳርድን በ17 ሚሊዮን ፓውንድ ለቤሺክታሽ የሸጠ ሲሆን፣ በምትኩ ክሪስቶ ጾሊስን በ34 ሚሊዮን ፓውንድ አስፈርሟል።

ሆኖም በቦታው ላይ የሚጫወተው ገብርኤል ማርቲኔሊ ባለፈው የፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ማስቆጠር የቻለው አንድ ግብ ብቻ በመሆኑ ቡድኑ ተጨማሪ አማራጭ ይፈልጋል።

በአሁኑ ወቅት በዓለም ዋንጫ ተሳትፎው ምክንያት በዕረፍት ላይ የሚገኘው ቪኒሲየስ፣ ከአዲሱ የሪያል ማድሪድ አሰልጣኝ ጆሴ ሞሪንሆ ጋር ያለው ግንኙነት ትኩረትስቦ ነበር። ምንም እንኳን ተጫዋቹ እና አሰልጣኙ ያለፉት ክስተቶች አልፈው አዲሱን የውድድር ዘመን በአዲስ መንፈስ ለመጀመር ዝግጁ እንደሆኑ ቢነገርም፣ የአርሰናል ፍላጎት ይፋ መሆን ግን የ2026/27 የውድድር ዘመንን በፕሪሚየር ሊጉ ሊጀምር እንደሚችል ጠንካራ ጥቆማ ሰጥቷል።



Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: