#Ethiopia | የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ ሞርጋን ሮጀርስን እና ኮል ፓልመርን በአንድ ሜዳ ላይ አጣምሮ ለማሰለፍ የሚያስችል ግልጽ ዕቅድ እንዳላቸው አስታወቁ።
አሰልጣኙ ሁለቱ ተጫዋቾች በአንድ ላይ ተሰልፈው ጥሩ ጥምረት ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ያላቸውን እምነት ገልጸው፣ “ለዚህ የሚሆን ዕቅድም ሆነ ሀሳብ አለኝ፤ ተጫዋቾቹ ድንቅ ጥምረት ሲፈጥሩ ይታየኛል” ብለዋል።
አክለውም በሜዳ ላይ ትክክለኛውን የተጫዋቾች ስብስብ እና ሚዛን መጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
“እነዚህን ልዩ ተጫዋቾች ትክክለኛው ቦታ ላይ በማሰለፍ እና ሚዛኑን በመጠበቅ ኳስን በመቆጣጠር ረገድ ይበልጥ ተወዳዳሪ መሆን እንችላለን፤ ኳስ በተጋጣሚ እግር ስር በሚሆንበት ጊዜም ጠንካራ መሆን ይጠበቅብናል” ሲሉ አብራርተዋል። የዣቢ አሎንሶ ይህ አዲስ ሐሳብም የሁለቱን ወጣት ኮከቦች ጥምረት በእጅጉ ተጠባቂ አድርጎታል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Source: GetuTemesgen









No comments yet.