ፆመ ፍልሰታን የፈረሰውን ቤተክርስቲያን ህንፃ በማስፈፀም በረከት እንድናገኝ ጥሪ ቀርቧል
በሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት በቀይት ወረዳ ሥር የሚገኘው የመለጥ ደብረ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ከተመሠረተ ከ60 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ታሪካዊ ቤተክርስቲያን ነው።
ነገር ግን እስካሁን እድሳት ባለመደረጉ ምክንያት ጣሪያው እያፈሰሰ ግድግዳው በስብሶ የቤተክርስቲያኑ ቋሚ ምሰሶዎች በምስጥ ተበልተው ቤተክርስቲያኑ ሊወድቅ ተቃርቦ በነበረበት ሰአት እናንተ ደጋግ ክርስቲያኖች ባደረጋችሁት እርዳታ የቤተክርስቲያኑን እድሳት ጀምረናል።
በመሆኑም ይህ ቤተክርስቲያን እድሳቱ በገንዘብ እጥረት ምክንያት ስለቆመ
ታቦቱን በጊዜያዊነት በማይመች ለታቦቱ ማረፊያ ብቻ ወደተዘጋጀች መቃኞ ስላለ ምእመናን በዝናብና በፀሐይ እያስቀደሰ ስለሆነ ቤተክርስቲያኑ ተጠናቆ ታቦታቱ ወደዋናው መቅደስ እንዲገቡ የእኛን ልጆቿን ድጋፍ ትሻለች
ስለዚህ በኢትዮጵያም ሆነ በውጭ አገር የምትኖሩ የቤተክርስቲያን ልጆች፣ በአቅማችሁ መጠን በመለገስ የእጣን፣ የጧፍ፣ የዘቢብ፣ በመርዳት ፆመ ፍልሰታን እንድናስቀድስ እንዲሁም የህንፃ ቤተክርስቲያናችንን እንድናስፈፅም የአቅማችሁን ድጋፍ እንድታደርጉልን እንጠይቃለን።
የድጋፍ አካውንት:
መለጥ ደብረ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን
1000756255626
ስልክ: 0920950007
የክርስትናስምዎን በመላክ አባቶች በፀሎት ያስቡዋችኋል









No comments yet.