በውጭ ሀገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርት አገልግሎት በቅርቡ እንደሚጀመር ተነገረ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገል…

- Advertisement -
Sidebar AD
በውጭ ሀገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርት አገልግሎት በቅርቡ እንደሚጀመር ተነገረ
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በውጭ ሀገራት ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ምቹ አሰራሮችን እየዘረጋ መሆኑን አስታውቋል።
ከእነዚህም መካከል አዲሱ የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርት  አገልግሎት በኤምባሲዎችና በቆንስላዎች በኩል በቅርቡ እንደሚጀመር ገልጿል።
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አምቦ መቃሳ እንደገለጹት፥ለዲያስፖራው የሚሰጠው አገልግሎት እንዲቀላጠፍ አዲስ ድረ-ገጽ ተዘጋጅቷል።
ይህ ድረ-ገጽ ተገልጋዮች ባሉበት ሀገር ሳይገደቡ የፓስፖርት እድሳትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በቀላሉ እንዲያከናውኑ የሚያስችል ነው ብለዋል።
የቢጫ ካርድ ባለቤቶች ቀደም ሲልም በሀገር ውስጥ ኢንቨስት የማድረግና የመንቀሳቀስ መብት ያላቸው በመሆኑ፤አዲሱ የጎልደን ቪዛ የግድ አስፈላጊ ላይሆን እንደሚችል ተጠቁሟል።
እነዚህ ቅርንጫፎች በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ በመሆናቸው፣ ተገልጋዮች ወደ አዲስ አበባ ሳይመጡ በአቅራቢያቸው አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ተብሏል።
ከፓስፖርት ባለፈም፣ የነዋሪነት ፈቃድና የቪዛ አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ በዲጂታል መንገድ እየተሰጡ ይገኛሉ ብለዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1