ኢትዮጵያ ለጅቡቲ የጭነት ተሽከርካሪዎች ማረፊያ የሚሆን መሬት ሰጠች
ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና የትራንስፖርት ኮሪደር ለማዘመን የሚያስችላቸውን ታሪካዊ ስምምነት በመተግበር በሞጆ ከተማ የመሬት ርክክብ ፈጸሙ።
ላለፉት 25 ዓመታት ዘግይቶ የቆየው ይህ ፕሮጀክት፣ ለጅቡቲ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪዎች ማቆሚያ ተርሚናል ግንባታ የሚውል መሬት ለጅቡቲ ወገን በመስጠት እውን ሆኗል።
በሞጆ ከተማ በተካሄደው የርክክብ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ፣ የጅቡቲ የመሠረተ ልማትና መሳሪያዎች ሚኒስትር ሳይድ ኑህ ሀሰን፣ የሞጆ ከተማ ከንቲባ እና የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተገኝተዋል።
ዓለሙ ስሜ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና በጅቡቲ ባለሥልጣናት መካከል በተደረገው ውይይት ውሳኔ ያገኘ ሲሆን፣ የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቁርኝት የበለጠ ያጠናክራል።
ለባህር በር አልባዋ ኢትዮጵያ ዋነኛ የንግድ መስመር የሆነው የሞጆ-ጅቡቲ ኮሪደር፣ አዲሱ የከባድ መኪኖች ማቆሚያ ተርሚናል ሲገነባበት በትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ይባክን የነበረውን ጊዜና ተጨማሪ ወጪ በእጅጉ ይቀንሰዋል ተብሏል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ እና ጅቡቲን የሚያገናኘውን የባቡር መስመር የጭነት አቅም እስከ እ.ኤ.አ. 2027 ወደ 6.2 ሚሊዮን ቶን ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ይታወቃል።
@Seledadotio
@Seledadotio
ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና የትራንስፖርት ኮሪደር ለማዘመን የሚያስችላቸውን ታሪካዊ ስምምነት በመተግበር በሞጆ ከተማ የመሬት ርክክብ ፈጸሙ።
ላለፉት 25 ዓመታት ዘግይቶ የቆየው ይህ ፕሮጀክት፣ ለጅቡቲ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪዎች ማቆሚያ ተርሚናል ግንባታ የሚውል መሬት ለጅቡቲ ወገን በመስጠት እውን ሆኗል።
በሞጆ ከተማ በተካሄደው የርክክብ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ፣ የጅቡቲ የመሠረተ ልማትና መሳሪያዎች ሚኒስትር ሳይድ ኑህ ሀሰን፣ የሞጆ ከተማ ከንቲባ እና የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተገኝተዋል።
ዓለሙ ስሜ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና በጅቡቲ ባለሥልጣናት መካከል በተደረገው ውይይት ውሳኔ ያገኘ ሲሆን፣ የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቁርኝት የበለጠ ያጠናክራል።
ለባህር በር አልባዋ ኢትዮጵያ ዋነኛ የንግድ መስመር የሆነው የሞጆ-ጅቡቲ ኮሪደር፣ አዲሱ የከባድ መኪኖች ማቆሚያ ተርሚናል ሲገነባበት በትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ይባክን የነበረውን ጊዜና ተጨማሪ ወጪ በእጅጉ ይቀንሰዋል ተብሏል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ እና ጅቡቲን የሚያገናኘውን የባቡር መስመር የጭነት አቅም እስከ እ.ኤ.አ. 2027 ወደ 6.2 ሚሊዮን ቶን ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ይታወቃል።
@Seledadotio
@Seledadotio
Related Posts
- Advertisement -








No comments yet.