* የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ ክልሎች እውቅና ተሰጥቷል
#Ethiopia | የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ባለፈው በጀት ዓመት ያከናወናቸውን አበይት ተግባራት የገመገመበትንና የቀጣይ የሦስት ዓመታት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ላይ የመከረበትን ሀገር አቀፍ የማጠቃለያ ሴክተር ጉባኤ ተካሄደ።
በጉባኤው ላይ የተገኙት የባህልና ስፖርት ሚኒስትሯ ክብርት ሸዊት ሻንካ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሕግ፣ በፖሊሲ እንዲሁም በባህልና ስፖርት ልማት ዘርፎች በርካታ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል።
ከእነዚህም መካከል ከ28 ዓመታት በኋላ የጸደቀው አዲሱ የስፖርት ፖሊሲና የትግበራ ማዕቀፍ፣ አዲሱ የስፖርት አዋጅ፣ የጥበባትና ፈጠራ ኢንዱስትሪ ረቂቅ ፖሊሲ እና የጥበብ ምክር ቤት ደንብና መመሪያዎች መዘጋጀታቸው በዋናነት ይጠቀሳሉ።
እነዚህ የፖሊሲ ማሻሻያዎች የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ፣ የስፖርት ኢኮኖሚውን በማጠናከርና በዘርፉ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቀረፍ ረገድ ጉልህ ድርሻ ይኖራቸዋል።
በተጨማሪም በባህል ዘርፍ 52 አገር አቀፍ፣ ሃይማኖታዊና የብሔር ብሔረሰቦች የዘመን መለወጫ ክብረ በዓላት በሰላም የተከበሩ ሲሆን፣ ከ46 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በመሳተፉ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን ለማጠናከር አስችሏል።
የንባብ ባህልን ለማስፋፋት በተደረገው አገር አቀፍ ንቅናቄ ከ24.9 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ተደራሽ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 454 ቤተ-መጻሕፍትን የማጠናከር ሥራ ተከናውኗል።
በኪነ ጥበቡ ዘርፍም የ”ኪን ኢትዮጵያ” ቡድን ሀገራዊ ባህልን ሲያስተዋውቅ፣ የሰርከስ ጥበብ ደግሞ 12 ዓለም አቀፍ ክብረወሰኖችን በመስበር ሀገርን ያስጠራበት ዓመት ነበር።
በስፖርቱ መስክ ደግሞ 49 ሺህ ታዳጊዎች በ1,550 የስልጠና ጣቢያዎችና በ36 ማዕከላት ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ፤ የመንግሥት ልዩ ትኩረት ያረፈባቸው ትላልቅ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ስታደየሞች ግንባታም ወደ መጠናቀቁ ተቃርቧል።
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በቀጣይ ዓመት ተቋማዊ ሪፎርምን በተሟላ መንገድ በመተግበር አገልግሎቶችን በዲጂታል ሥርዓት ለማዘመን ማቀዱ የተገለጸ ሲሆን፣ በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ግለሰቦች እና ተቋማት እውቅና ተሰጥቷል።
በዚህም መሠረት በባህልና ኪነጥበብ ዘርፍ
1. የአማራ ባህል ቱሪዝም ስፖርት ቢሮ
2. የኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ
3. አዲስ አበባ ባህልና ኪነጥበብ ቢሮ
በስፖርት ዘርፍ
1. የኦሮሚያ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ
2. .የአዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ
3. የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ስፖርት ቢሮ ተሸላሚ ሆነዋል።
እንዲሁም ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከአራቱ ተጠሪ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ጸረ አበረታች ቅመም ባለስልጣን የልዩ ተሸላሚነት እውቅና አግኝተዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#MinistryOfCultureAndSport
#EthiopiaMoCS #Ethiopia #EthiopianNews



Source: GetuTemesgen









No comments yet.