#Ethiopia | አዲስ አበባ — የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ባወጣው አዲስ የአደጋ ሥጋት ደኅንነት መመሪያ መሠረት፣ ግንባታቸው ሳይጠናቀቅና የደኅንነት ማረጋገጫ ሳያገኙ ሕንፃዎችን ለአገልግሎት የሚያከራዩ አካላት ላይ የ100 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣትና የወንጀል ተጠያቂነት እንደሚጣል አስታወቀ።
ኮሚሽኑ እንዳመለከተው፣ ይህ ጠንካራ እርምጃ የተወሰደው ያልተጠናቀቁ ሕንፃዎች በዜጎች ሕይወትና ንብረት ላይ የሚያደርሱትን ከፍተኛ የአደጋ ሥጋት በዘላቂነት ለመከላከልና ለመቀነስ ታስቦ ነው።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ አዲሱ መመሪያ በግንባታ ቦታዎች ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመቅረፍ የሚከተሉትን ነጥቦች በጥብቅ ከልክሏል፡
የሠራተኞች ደኅንነት፡ በግንባታ ወቅት ለሠራተኞች የሚያስፈልጉ የደኅንነት መጠበቂያ ቁሳቁሶችን አለማሟላት፣
የጉድጓዶች ደኅንነት፡ የተቆፈሩ ጉድጓዶችን አለመከለልና የጥንቃቄ ማስጠንቀቂያ ምልክት አለማድረግ፣
የሥራ ቁሳቁስ ጥራት፡ ጠንካራ ያልሆኑና ለአደጋ የሚያጋልጡ የማደላደያ ቁሳቁሶችን (Scaffolding) መጠቀም፣
የቆሻሻና አፈር አወጋገድ፡ በቀላሉ ሊደረመሱ የሚችሉ አፈርና የግንባታ ተረፈ ምርቶችን አደጋ በሚፈጥር ሁኔታ በሥፍራው ማከማቸት።
አዲሱ መመሪያ የግንባታ ባለቤቶችና ተቋራጮች የደኅንነት መስፈርቶችን አክብረው እንዲሠሩና የዜጎችን ደኅንነት እንዲጠብቁ የሚያስገድድ ነው።
Source: GetuTemesgen








No comments yet.