“ከጭቃ ጎጆ እስከ ነጩ ቤተመንግስት
#Ethiopia | በዓለም ታሪክ ውስጥ የብዙ ታላላቅ መሪዎች ሥራ ፈጣሪዎችና ስኬታማ ሰዎች የሕይወት መሪ የሆነች አንዲት ድንቅ አባባል አለች።
በአሜሪካ አስቸጋሪ ጊዜያት አገራቸውን ከውድቀት የታደጉትና የባርነትን ሥርዓት የሻሩት የቀድሞው ፕሬዚዳንት አብርሃም ሊንከን የተናገሯት ይህች አባባል ናት።
ይህ አባባል በውስን ቃላት ብቻ የተቋጠረ ቢሆንም በውስጡ ግን የዕድሜ ልክ ጥበብን አቅፎ ይዟል።
የሚል
ብዙዎቻችን በሕይወታችን ውስጥ ትልቅ ቦታ ወይም ስልጣን ካላገኘን ስኬታማ እንደማንሆን አድርገን እናስባለን።
የአብርሃም ሊንከን መልእክት ግን ይህንን አስተሳሰብ ሙሉ በሙሉ ይሰብራል።
ሊንከን እንደሚነግረን የስኬት ምስጢሩ በያዝነው ቦታ ወይም ማዕረግ ላይ ሳይሆን ባለንበት ቦታ ላይ በምንሰጠው የጥራት ደረጃ እና ቁርጠኝነት ላይ ነው።
ሊንከን ራሱ የተወለደው በኬንታኪ ከሚገኝ የጭቃ ጎጆ ውስጥ ሲሆን መደበኛ ትምህርት እንኳን ሳይማር በራሱ ጥረት በማንበብ ለታላቅነት የበቃ ሰው ነው።
እሱ ያመነው በማንኛውም ሥራ ውስጥ የተሰማራ ሰው ነጋዴ፣ ተማሪ፣ ሹፌር፣ መምህር፣ ጽዳት ወይም የሀገር መሪ የተሰጠውን ኃላፊነት በጥራት እና በታማኝነት ከተወጣ የዓለምን ትኩረት መሳቡ አይቀሬ መሆኑን ሊንከን ያምናል።
የሚያበራው የወርቅ ማዕረግ ሳይሆን የምታሳየው የላቀ ብቃት ነው።
የተቀበልከውን ትንሽ ሀላፊነት በልዩ ብቃት ስታከናውን ታላላቅ በሮች ይከፈቱልሃል ይላል።
ከሰዎች ሙገሳና ምስጋና ይልቅ ለራስህ መርህና ለእውነት ታማኝ መሆን የዘላቂ ስኬት መሠረት ነው።
ሊንከን በንግድ ከስሯል በምርጫ ተሸንፏል ነገር ግን በሄደበት መንገድ ሁሉ ምርጡን ለመስጠት በመጣሩ ውድቀቶቹ ለታላቅ ፕሬዚዳንትነት ማዕረግ አበቁት።
ዛሬ ላይ ቆመህ ህይወቴ ወዴት እየሄደ ነው ብለህ የምትጠይቅ ከሆነ መልሱ በእጅህ ላይ ይገኛል።
የምታደርገውን እያንዳንዷን ትንሽ ነገር በጥራት በፍቅር እና በታማኝነት አከናውናት።
ምክንያቱም ታሪክ የሚያስታውሳቸው ያገኟቸውን አጋጣሚዎች ሁሉ ምርጥ እና ድንቅ አድርገው የተጠቀሙበት ሰዎች ብቻ ነውና።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#Ethiopia #GetuTemesgen
#Usa #president #lifestyle
#AbrahamLincoln #politics
#Goldensaying #history
Source: GetuTemesgen








No comments yet.