🎼
#Ethiopia | በሀገራችን የድራም ሙዚቃ አጨዋወት ታሪክ ውስጥ ስማቸው በገነነው የሙዚቃ ባለሙያ ቴዎድሮስ አምዴ የተቀናበረውና 11 የኢትዮ-ጃዝ ሙዚቃዎችን የያዘው «ምስክር» የተሰኘ አዲስ አልበም በመጪው አርብ በናሆም ሬከርድስ የYouTube ቻናል በይፋ ለአድማጮች ይበቃል።
ይህ አልበም ለጥናት፣ ለዝግጅትና ለፈጠራ ሂደቱ በአጠቃላይ 16 ዓመታትን የፈጀ ሲሆን፣ ለሀገራችን የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ልዩና አዲስ ኦሪጅናል የጃዝ ሥራ እንደሆነ ተገልጿል።
በአልበሙ ላይ 8 ታዋቂ የቤዝ ጊታር ተጫዋቾችን (አብይ ሰለሞን፣ ሄኖክ ተመስገን፣ ዳግማዊ አሊ እና ሌሎችንም) ጨምሮ በሊድ ጊታር፣ ኪቦርድ፣ ትሮምቦን እና ፍሉት የታወቁ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል።
በተጨማሪም የሙዚቃ ባለሙያው ቴዎድሮስ አምዴ፣ የደብል ቤዝ ድራም አጨዋወትን ያለ አስተማሪ ለመማር የሚያስችል ባለ 218 ገጽ መጽሐፍ አዘጋጅቶ ለአንባቢዎች ያቀረበ ሲሆን፤ መጽሐፉ በአብርሆት ቤተ መጻሕፍትና በያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ይገኛል።
ልዩ መታሰቢያ፡
ይህ አልበም በሥራው ዝግጅት ወቅት አብረው ለሠሩትና አሁን በሕይወት ለሌሉት ታዋቂው የትራምፔት ተጫዋች ሻምበል መኮንን መርሻ እና የቤዝ ጊታር ተጫዋች ፋሬው መንግስቱ መታሰቢያነት የተበረከተ ነው።
#EthioJazz #TewodrosAmde #MeskirAlbum #NahomRecords #EthiopianMusic #DoubleBassDrum
Source: GetuTemesgen









No comments yet.