#FastMereja I በኢትዮጵያ በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ አካላዊና ሥነ-ልቦናዊ ጥቃቶች እንዲሁም የሕይወት ህልፈት የሚያስከትሉ ጥቃቶች አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሳቸውን በመግለጽ፣ መንግሥት ጉዳዩን እንደ ብሔራዊ ቀውስ በመቁጠር አስቸኳይና መዋቅራዊ እርምጃ እንዲወስድ የሚጠይቅ ሀገር አቀፍ የፊርማ ማሰባሰብ ዘመቻ (#ትሰማ / #TISEMA) ተጀምሯል።
በማኅበራዊ ሚዲያና በዲጂታል አማራጮች አማካይነት እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ ዘመቻ፣ በቅርብ ዓመታት በየአካባቢው በሴቶችና ህፃናት ላይ የተፈጸሙ ጭካኔ የተሞላባቸው ጥቃቶችና የግድያ ድርጊቶች የታየባቸው ሂደት ሕግን የማስከበር ሥርዓቱ አሁንም ከፍተኛ ክፍተት እንዳለበት የሚያሳይ ነው ተብሏል። አዘጋጆቹ እንደሚሉት፣ ጥቃት አድራሾች በበቂ ሁኔታ አለመቀጣታቸው፣ የምርመራ ሂደቶች መጎተትና የማስረጃ መጥፋት ክስተቶች የፍትሕ ሥርዓቱን እያደናቀፉት ይገኛሉ።
አክቲቪስቶችና የመብት ተሟጋቾች መንግሥት ጥቃቱን እንደ ብሔራዊ ቀውስ አውጆ ጥብቅ የሕግ ማዕቀፍ እንዲዘረጋ፣ ለጥቃት ሰለባዎች የሚደረጉ የሕክምና፣ የሥነ-ልቦና እና የሕግ ድጋፎችን እንዲያጠናክር፣ እንዲሁም ወንጀለኞች ተመጣጣኝና ጠንካራ ቅጣት እንዲያገኙ ጥሪ አቅርበዋል። የሕዝብ ተሳትፎውና የፊርማ ማሰባሰቡ ሂደት አሁንም በስፋት ቀጥሎ ይገኛል።
Source: FastMereja









No comments yet.