* ፖሊስ ህብረተሰቡ የትብብር ድጋፍ እንዲያደርግ ጠየቀ
#Ethiopia | በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 ክልል ልዩ ቦታው ብስራተ ኤልያስ አካባቢ የሚኖረው የ18 ዓመቱ ወጣት ኤልያስ ገበየሁ ታዬ ከቤት እንደወጣ ሳይመለስ መቅረቱን የአካባቢው ፖሊስ መሪያ ቤት አስታውቋል።
አባቱ አቶ ገበያሁ ታዬ በገጃ ሰፈር አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው ባስመዘገቡት አቤቱታ መሰረት፣ ወጣቱ በ19/12/2018 ዓ.ም ከቤት የወጣ ሲሆን እስካሁን ድረስ ያለበት ቦታ አልታወቀም። ጉዳዩ በሁነት ማጣሪያ መዝገብ ቁጥር 02/18/19 ተመዝግቦ የፍለጋ እና የክትትል ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
የልደታ ዋና ፖሊስ መምሪያ የወንጀል እና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ክፍል የጠፋውን ወጣት ፎቶግራፍ በመበተን በቴሌቪዥንና በሌሎች መገናኛ ብዙኃን እንዲተላለፍ እና ህብረተሰቡ መረጃ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ አቅርቧል።
ወጣቱን ያየ፣ ያለበትን የሚያውቅ ወይም ማንኛውንም ጠቃሚ መረጃ ያለው ሰው በሚከተሉት የፖሊስ ስልክ ቁጥሮች በመደወል ትብብር እንዲያደርግ ጠየቋል፦
የገጃ ፖሊስ ጣቢያ መረጃ ስልክ፡ 0112300436
የልደታ ዋና ፖሊስ መምሪያ፡ 0116556150
የፈላጊ ቤተሰቦቹ ስልክ ቁጥር
0935871945
0962211918
0911780839
#ሼር # Share
#MissingPerson #Ethiopia #AddisAbaba #LidetaSubcity #HelpFindSeysay



Source: GetuTemesgen







No comments yet.